
ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 17ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ሲጀምሩ በምድብ ሀ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ከተማ፤ በምድብ ለ አዳማ እና ሀላባ አሸንፈዋል።
በምድብ ለ አዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም አዳማ ከተማን ከአዲስ አበባ ከተማ ያገናኘው ወሳኝ ጨዋታ በአዳማ ከተማ የ2-0 በሆነ ውጤት አሸናፊነት ተጠናቋል። አዳማ ከተማ የነጥበረ ልዩነቱን ለማጥበብ፣ አዲስ አበባ ከተማ ደግሞ የምድብ አሸናፊነቱን ለማረጋገጥ እንዲሁም ሁለቱም ቡድኖች የሚከተሉት በኳስ ቁጥጥር ላይ የተመሰረተ የጨዋታ አቀራረብ ጨዋታውን ተጠባቂ አድርጎታል።
እንደተጠበቀው በርካታ የግብ ዕድሎች የተፈጠሩበት መልካም የሚባል የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ተመልከትንበት የተጠናቀቀ ጨዋታ ሆኖ አልፏል። ብዙም ሳይቆይ ነው ገና በጨዋታ ጅማሬ 1ኛው ደቂቃ በአዲስ አበባ ግብ ጠባቂ ዮሴፍ ወንድማገኝ እና ተከላካይ ኢያሱ ለገሰ መካከል በተፈጠረ አለመግባት የተነሳ እያሱ ለገሰ በራሱ ላይ ባስቆጠረው ጎል አዳማዎች ቀዳሚ የሆኑት። በበፍጥነት የዚች ጎል መቆጠር የአዲስ አበባ ተጫዋቾችን እንዳይረጋጉ ሲያደርግ አዳማዎችን ጎሏ አነቃቅታቸዋለች። በመሐል ሜዳ ላይ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የወሰዱት አዳማዎች የአዲስ አበባ የተከላካዮችን መዘናጋት ተከትሎ ተጨማሪ ጎል ማስቆጠር የሚችሉበትን ነፃ የጎል አጋጣሚ ዮሐንስ ፈንታ ሳይጠቀምበት የቀረው የሚያስቆጭ ነው። ኳሳቸው እየተቆራረጠ የተቸገሩት አዲስ አበባዎች ተረጋግተው ወደ ጨዋታው በመግባት አላዛር ሽመልስ ከቀኝ መስመር ተከላከይ በማለፍ ያሻገረውን ብሩክ ሰሙ አግኝቶ ወደ ጎል በቀጥታ ቢመታውም ለጥቂት ወደ ውጭ ወጥቶበታል።
U-20 | ቅዱስ ጊዮርጊስ በምድብ ሀ መሪነቱ ሲቀጥል በምድብ ለ አዳማ ልዩነቱን አጥብቧል
