የሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነትን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ፎረም ተቋቋመ

የFBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) ምስል

የሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነትን በተግባቦትና ህዝብ ግንኙነት ስራዎች ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ፎረም ተቋቋመ።

ፎረሙ በቃል ኪዳኑ መሰረት ስርዓተ ምግብ እና ጤናን በማሻሻል ከሁለት ዓመት በታች የህፃናት የመቀንጨር ችግርን በ2022 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የሚደረገውን ሐገራዊ ጥረት በተግባቦት እና ህዝብ ግንኙነት ስራዎች ለማገዝ ያለመ ነው ተብሏል።

የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ የሰቆጣ ቃል ኪዳን ስምምነት በተለያዩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት በቅንጅት እየተሰራበት መሆኑን ተናግረዋል።

የቃል ኪዳኑን ግብ ከዳር ለማድረስም በምግብና በስርዓተ ምግብ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ የተግባቦትና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑን ገልፀዋል።

የመቀንጨር ችግር በሀገር ደረጃ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስና የባህሪ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ ጠንካራ የተግባቦት ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ መከወን እንደሚገባ ጥሪ መቅረቡን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

https://fanabc.com/2019/06/የሰቆጣ-ቃል-ኪዳን-ስምምነትን-ውጤታማ-ማድ/

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started
search previous next tag category expand menu location phone mail time cart zoom edit close